“ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር በቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

በቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው መርሃ ግብር ላይ የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት (ተጠባባቂ) ኢን. አብዲፈታህ አህመድ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች አቶ አብዲሰላም አብዱላሂ፣ አቶ በሺር ዩሱፍ፣ አቶ አህመድ አብዲናሲር እና ዳይሬክተሮች፣ ኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ መምህራን፣ የአስተዳደርና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እና የግቢው የፀጥታና ደህንነት አስከባሪ ሰራተኞችን ጨምሮ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዬች በተገኙበት ተካሂዳል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ ሁሉም አካላት ለሀገር ለመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብር በመግለፅ ከሰራዊቱ ጎን መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ

ህዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም